Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

መከላከያ ሰራዊቱን በመቀላቀል እና ስልጠና በመውሰድ ሀገራችንን እጠብቃለን- የመቄት ወረዳ ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በፋላቂት ከተማ የመቄት ወረዳ ነዋሪዎች ከተለያዩ ቀበሌዎች የተውጣጡ በርካታ ነዋሪዎች የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊትን ለመቀላቀል እና ስልጠና ለመውሰድ በነቂስ ወጥዋል።
የህወሓት የሽብር ወረራ ከፈፀመባቸው አካባቢዎች የመቄት ወረዳ አንዱ ሲሆን፥ ቡድኑ በቆየባቸው አንድ ወር ከአስር ቀናት ውስጥ በርካታ ኢሰብአዊ ድርጊቶቹን በመፈፀሙ ነዋሪዎቹ ለከፍ ችግር ተጋልጠዋል።
በዚህም ዛሬ በፍላቂት ከተማ በሺህዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች መከላከያ ሰራዊቱን ለመቀላቀል እና ስልጠና ለመውሰድ ወጥተዋል።
ይህንንም በማድረግ ሀገራችንን እጠብቃለን ያሉት ነዋሪዎቹ፥ ከዚህ በላይ ምንም ችግር እና መከራ ሊደርስብን አይችልም ሲሉ ገልጸዋል።
የሽብር ቡድኑን የፈፀመውን አስነዋሪ ድርጊት በእጅጉ እንዳስከፋቸው ተናግረዋል።
በምንይችል አዘዘው
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version