የሀገር ውስጥ ዜና

ለአሸባሪዎች ድጋፍ በማድረግ ወንጀል በተጠረጠሩ 15 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ

By Feven Bishaw

September 16, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረሪ ክልል ለአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ድጋፍ በማድረግ ወንጀል በተጠረጠሩ 15 ግለሰቦች ላይ ክስ መመስረቱን የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ።

የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዋና አቃቤ ህግ አቶ አዩብ አህመድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጁትን ህወሓት እና ሸኔን በክልሉ የሚደግፉ ግለሰቦችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከህብረተሰቡ እና ጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው።