የሀገር ውስጥ ዜና

የቡና አመራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፎረም ተካሄደ

By Feven Bishaw

September 16, 2021

አዲስ አበባ ፣መስከረም 6፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቡና አምራች አርሶ አደሮችን ፍትሐዊና ተጠቃሚ የሚያደርግ “የአፍሪካ ተጠቃሚነት ድርጅት ፎረም 2021” በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ ተካሄደ፡፡

በፎረሙ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የንግድ ማስፋፊያ ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ አምባሰደር ምስጋኑ አርጋ÷ ቡና የአገሪቱ የወጪ ንግድ ገቢ 25 በመቶ በማስገኘት ለኢትዮጵያ የገቢ ምንጭ ከመሆኑም ባሻገር ለ26 ሚሊየን ህዝብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመዋል ፡፡