የሀገር ውስጥ ዜና

የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ለህልውና ዘመቻው ድጋፍ አደረገ

By Meseret Awoke

September 13, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014፣ (ኤፍ ቢ ሲ) የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ልዑካን ቡድን ወሎ ግንባር በመገኘት ለመከላከያ ሰራዊቱ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ፡፡

የዩኒቨርሲቲው ልዑካን ቡድን በወሎ ግንባር በመገኘት አስር ሰንጋዎችን ለመከላከያ ሰራዊት በስጦታ አበርክቷል፡፡

ድጋፉም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የአንድ ወር ደመወዙን በመለገሱ የተገኘ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከአሁን ቀደምም ለህልውና ዘመቻው የተለያየ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቁሞ÷ በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!