Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ለህልውና ዘመቻው ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014፣ (ኤፍ ቢ ሲ) የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ልዑካን ቡድን ወሎ ግንባር በመገኘት ለመከላከያ ሰራዊቱ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ፡፡

የዩኒቨርሲቲው ልዑካን ቡድን በወሎ ግንባር በመገኘት አስር ሰንጋዎችን ለመከላከያ ሰራዊት በስጦታ አበርክቷል፡፡

ድጋፉም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የአንድ ወር ደመወዙን በመለገሱ የተገኘ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከአሁን ቀደምም ለህልውና ዘመቻው የተለያየ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቁሞ÷ በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version