አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አንጋፋው ድምፃዊ ዓለማየሁ እሸቴ ሀገሩን በቅንነት ያገለገለና በታላቅ ፍቅር ዘመን ተሻጋሪ የሆኑ በርካታ የጥበብ ስራዎችን የሰራ ኢትዮጵያዊ ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡
ምክትል ከንቲባዋ የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ አንድ ደረጃ ከፍ ያደረገዉን፣ ኢትዮጵያን ሳይሰስት ያገለገለውን፣ አንጋፋዉን የጥበብ ሰዉ አርቲስት አለማየሁ እሸቴን ዛሬ በክብር ተሰናብተነዋል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል፡፡