የሀገር ውስጥ ዜና

አጣዬና አካባቢው እንዳይረጋጋ የሚሰሩ አካላትን ከህወሓትና ሸኔ እኩል መታገል ይገባል-ዶ/ር አህመዲን

By Melaku Gedif

September 06, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አጣዬና አካባቢው እንዳይረጋጋ የሚሰሩ አካላትን ከህወሓትና ሸኔ የሽብር ቡድኖች እኩል መታገል እንደሚገባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አህመዲን መሐመድ ገለጹ፡፡

የአጣዬ ከተማ ወጣቶች በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአካባቢው ኮማንድ ፖስት፣ ከፌደራልና ከክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡