Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሴቶች የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን የሴካፋ ሻምፕዮንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታውን ዛሬ ያካሂዳል፡፡
መርሃ ግብሩ እንደሚያሳየው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግርኳስ ቡድን ከኡጋንዳው አቻው ሌዲ ዶቭስ ኤፍሲ ጋር ይጫወታል፡፡
በዚሁ መሠረት ከ10፡00 ሰዓት ጀምሮ ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ ተብሏል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ያለፉትን ሦስት ጨዋታዎች 4 ለ2፣ 10ለ1 እንዲሁም 10ለ0 ማሸነፉን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version