የሀገር ውስጥ ዜና

በሀዲያ ዞን የሚገኙ የትምህርት ተቋማት ለሀገር መከላከያ ሠራዊት 18 ሰንጋዎችን ድጋፍ አደረጉ

By Feven Bishaw

September 05, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በሀዲያ ዞን የሚገኙ 15 የግልና 5 የመንግስት የትምህርት ተቋማት ለሀገር መከላከያ ሠራዊት 18 ሰንጋዎችን ድጋፍ ማድረጋቸዉን የዞኑ ቴክኒክና ሙያ መምሪያ አስታወቀ።

በሀገር ላይ የተደቀነዉን የህልዉና አደጋ ለመመከት በቀጣይም ለመከላከያ ሠራዊት ያላቸዉን አጋርነት እንደሚገልጹ ተቋማቱ ገልጸዋል።