Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና ሰራተኞች ለመከላከያ ሠራዊት ደም ለገሡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና ሰራተኞች ለመከላከያ ሠራዊት ደም ለገሱ።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር አስራት አፀደወይን ተቋሙ የህልውና ዘመቻው እንዲሳካ በተለያየ መልኩ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

አሸባሪው የህወሀት ቡድን ከማይካድራ ጀምሮ በደቡብ ጎንደርና መተከል የፈፀማቸውን ግፎች በተመለከተ ዩኒቨርሲቲው ጥናትና ምርምሮችን እያደረገ ስለመሆኑም ገልፀዋል።

የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞችና አመራሮች በመጀመሪያው ዙር የደሞዛቸውን ከ10 እስከ 30 በመቶ ለመከላከያ ሠራዊት ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም በሁለተኛው ዙር ደግሞ የ1 ወር ደሞዛቸውን ከ54 ሚሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ እና በመለገስ ድጋፍ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

Exit mobile version