የሀገር ውስጥ ዜና

በሻሸመኔ ዘመናዊ የመብራት ምሰሶዎች አገልግሎት እየሰጡ አይደለም- ነዋሪዎች

By Feven Bishaw

September 03, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሻሸመኔ ከተማ ከ2007 ዓ.ም. ጀምሮ የተገነቡት ዘመናዊ የመብራት ምሰሶዎች አስፈላጊውን አገልግሎት እየሰጡ አለመሆኑን ነዋሪዎች ቅሬታቸውን አቀረቡ።

ነዋሪዎቹ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት ÷ምሰሶዎቹ የከተማዋን ውበት ከማድመቅ ውጪ አገልግሎት እየሰጡ አይደለም ።