Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ለህልውና ዘመቻው በግንባር በመገኘት ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በደሴ ከተማ የሚኖሩ የተለያየ ማሕረሰብ ተወካዮች ግንባር ድረስ በመሄድ የስንቅ ድጋፍ አድርገዋል፡፡

የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ለሠራዊቱ ያላቸውን ደጀንነት ለማሳየት በተወካዮቻቸው አማካኝነት በግንባር በመገኘት ባስረከቡበት ወቅት÷ አረመኔው የሽብር ቡድን እስከሚደመሰስ ድረስ ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የመከላከያ ሰራዊት አመራር አባላት በበኩላቸው÷ የደሴ ከተማ ህዝብ ደጀንነቱን ለማስመስከር ያደረገውን ድጋፍ አድንቀው÷ ድጋፉም ከድጋፍነት የተሻገረ ትርጉም ያለው እንደሆነና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡

ይኸው ድጋፍም አሸባሪውን የህወሓት ቡድን በመደምሰስ ሂደት ከፍተኛ የሞራል ስንቅ እንደሚሆናቸው ነው የተናገሩት፡፡

ድጋፉን ለማድረስ ግንባር ድረስ የተገኙ የከተማዋ ነዋሪ ተወካዮችም÷ ከምንም በላይ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለሀገር ህልውና እየከፈለ ያለውን ዋጋ መመልከታቸውን ገልፀዋል፡፡

 

 

በሐብታሙ ተክለሥላሴ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version