የሀገር ውስጥ ዜና

ኮሚሽኑ ለተፈናቃይ ወገኖች የምግብ እና የቁሳቁስ ድጋፎችን ተደራሽ ለማድረግ እየሠራ መሆኑን ገለጸ

By ዮሐንስ ደርበው

September 02, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሔራዊ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን እና የአማራ ክልል አደጋ መከላከል፣ ምግብ ዋስትና እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎች በደሴ ከተማ የተጠለሉ ተፈናቃይ ወገኖች ያሉበትን ሁኔታ ጎብኝተዋል።

ከሰሜን ወሎ ዞን በአሸባሪው የትህነግ ቡድን የተፈናቀሉ ወገኖች በደሴ ከተማ ተጠልለው ይገኛሉ።