የሀገር ውስጥ ዜና

በሀረሪ ክልል የሚካሄደው ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው

By Feven Bishaw

August 31, 2021

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀረሪ ክልል የሚካሄደው ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ የሚገኙ የመንግስትና የፀጥታ አካላት አመራሮች በክልሉ የሚካሄደው ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡