አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ ከአሸባሪው የህውሓት ቡድን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው 78 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑ ተገለጸ፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ፓሊስ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር አየልኝ ታክሎ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷የጁንታው ተላላኪዎች ወደ ከተማዋ ሰርገው በመግባት የሽብር ጥቃት እንዳይፈጽሙ ጠንካራ የኬላ ፍተሻና የጸጥታ ስራ እየተከናወነ ነው፡፡