Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሂቺሌማ የቀድሞ ሹማምንቶችን አሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲሱ የዛምቢያ ፕሬዚዳንት ሃካይንዴ ሂቺሌማ የሀገሪቷን ከፍተኛ የጦር ሹማምንት እና የፖሊስ ኃላፊ በአዳዲስ መተካታቸው ተሰማ፡፡

የፕሬዚዳንቱ እርምጃ የፀጥታ አካላት ለዜጎች የበለጠ ኃላፊነት ተሰምቷቸው ስራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል፡፡

የሃገሪቱን አዲስ የጦር፣ አየር ኃይል እና ብሔራዊ አገልግሎት ሹማምንቶቻቸውን እና ምክትሎቻቸውን እንዲሁም የፖሊስ ሃላፊዎችን ይፋ አድርገዋል፡፡

ሂቺሌማ አዲሶቹ የቢሮ ኃላፊዎች የዜጎችን ሰብአዊ መብት እና ነፃነት በማክበር ሀገራቸውን በትጋት እንዲያገለግሉም ጥሪ አቅርበዋል።

ፖሊሶች ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ከመዋላቸው በፊት አስፈላጊውን ፍተሻ እና የማጣራት ስራ ማከናወን እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡

ሁሉም የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች ከኃላፊነታቸው ቢነሱም ተተኪዎቻቸው ግን አልተገለፁም።

በከፍተኛ ድምፅ የተመረጡት የአሁኑ የዛምቢያ ፕሬዚዳንት ቀደም ሲል በፖሊሶች ከፍተኛ ድብደባ ሲደርስባቸው እንደነበር እና ለበርካታ ጊዜያት በእስር እንደቆዩ ቢቢሲ አስታውሷል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version