አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 23፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ልማት ማህበር ከ1 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተደረገበት 220 ኩንታል የስንዴ ዱቄት በንፋስ መውጫ ለተጎዱ ነዋሪዎች ድጋፍ አድርጓል።
የማህበሩ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አራጋው ታደሰ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንዳሉት የህወሓት አሸባሪ ቡድን የንፋስ መውጫ ከተማን ተቆጣጥሮ በነበረበት ወቅት ንጹሃን ዜጎችን በመግደል፣ ሃብትና ንብረት በመዝረፍና በማውደም ህብረተሰቡ ለእለት ምግብ እጦት እንዲጋለጥ አድርጓል።