ስፓርት

ፌዴሬሽኑ በአረንጓዴ አሻራ የንቅናቄ መርሃ ግብር ላይ ተሳተፈ

By Alemayehu Geremew

August 28, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በግብርና ሚኒስቴር በተጠራው “ኑ ኢትዮጵያን አረንጓዴ እናልብሳት” በሚል መሪ ቃል የሚከናወን የንቅናቄ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተሳታፊ ሆኗል፡፡

በፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የተመራው የስራ አስፈፃሚና ማኔጅመንት ኮሚቴ አባላት፣ እንዲሁም ታዋቂ አትሌቶችና አሰልጣኞችን የያዘ ልኡክ በዛሬው ዕለት በቢሾፍቱ ዋና ዋና ጎዳናዎች በመዘዋወር ንቅናቄ የመፍጠር ተግባራት አከናውኗል፡፡

ፌዴሬሽኑም በነገው ዕለት በሚካሄደው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ላይ እንደሚሳተፍ ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡