Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አሸባሪው ህወሓት ዳሎልን ለመቆጣጠር ያደረገው ሙከራ በአፋር ልዩ ሀይል እና ሚሊሻ ከሸፈ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 22 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው ህወሓት በአፋር ክልል ዳሎልን ለመቆጣጠር ያደረገው ሙከራ በአፋር ክልል ልዩ ሀይል እና ሚሊሻ ከሽፏል፡፡

ህወሓት በክለሉ በበርሃሌ ወረዳ በርካቶችን ገድሏል፣ አቁሱሏል፣ ከቤት ንብረታቸውም አፈናቅሏል እንዲሁም ቅርሶችን አውድሟል፡፡

ቡድኑ በከባድ መሳሪያ ጥቃት ቢፈጽምም የአፋር ልዩ ሃይል አባላት ባላቸው አነስተኛ መሳሪያ በማጥቃት ትልቅ ጀብድ እንደፈጸሙ የዞን 3 ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አሊ በስፍራው ለሚገኘው ባልደረባቸን ነግረውታል፡፡

አሁን ላይም ልዩ ሃይሉ ከፍተኛ ድል እያስመዘገበ ነው ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው፡፡

በአሸባሪው ቡድን ከቀያቸው የተፈናቀሉ ከ6 ሺህ በላይ ዜጎች ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን የገለጹት አቶ መሀመድ፥ ድጋፉ በቂ ባለመሆኑ ትኩረት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

በጌታሰው የሺዋስ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version