Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የህወሓት ተላላኪዎች ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደባቸው ነው

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ለህወሃት የሚላላኩ የውስጥ ባንዳዎችን ለይቶ በማውጣት አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደባቸው መሆኑን የደቡብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ገለፀ።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቀለምወርቅ ምህረቴ ከንግዱ ማህበረሰብ እና ከዞኑ ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እያካሄዱ እንደሆነም ታውቋል፡፡

የህወሓት የሽብር ቡድን በደቡብ ጎንደር ዞን በፈፀመው ወረራ በርካታ ጥፋቶችን እንዳደረሰ አስተዳዳሪው ጠቁመው፥ ከጦርነቱ የበለጠ የውስጥ ባንዳዎች የሚሰጡት መረጃ ከፍተኛ ጉዳት እንዳስከተለ ገልፀዋል፡፡

በዘመቻውም የንግዱ ማህበረሰብ ለሰራዊቱ ደጀን በመሆን ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የሀሰት መረጃ በሚያሰራጩ ሰርጎ ገቦች ላይም እርምጃ እየተወሰደባቸው እንደሆነና በርካታ ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጣራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

የስብሰባው ተሳታፊዎች አሸባሪውን ህወሓት ለመዋጋት ግንባር ቀደም የነበሩትን የተሳሳተ ስም በመስጠት ትግሉን የሚጎትቱ ባንዳዎች ሊለቀሙ ይገባል ብለዋል።

በዙፋን ካሳሁን እና ምንይችል አዘዘው

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version