Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኬንያ አስጎብኚዎች እና የጉዞ ወኪሎች ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ የኬንያ አስጎብኚ ድርጅቶች፣ የጉዞ ወኪሎች፣ የሳፋሪ ባለሙያዎች እና ጋዜጠኞች የኢትዮጵያን ታሪካዊ የቱሪስት መዳረሻዎች ይጎበኛሉ።

እነዚህ አስጎበኚዎች እና ጋዜጠኞች የኢትዮጵያን የቱሪስት መስህቦችን በማስተዋወቅ እና ለቱሪስቶች በመሸጥ እንዲሁም የኢትዮጵያ በጎ ገፅታ ለኬንያ እና ለሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ያስተዋውቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በፈረንጆቹ ከነሀሴ  28 እስከ 31 ቀን 2021  የሚደረገውን ይህንን ጉብኝት ያዘጋጁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ቱሪዝም ኢትዮጵያ በጋራ በመተባበር ነው።

በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ ዓለም በሰጡት ገለፃ፥ የጉብኝቱ ዓላማ እየተጠናከረ የመጣውን የኢትዮጵያ እና ኬንያ የንግድ ትስስርን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ነው ማለታቸውን ኬንያ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version