የሀገር ውስጥ ዜና

በፓሪስ አሸባሪው ህወሓትን የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሄደ

By Feven Bishaw

August 25, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንሣይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራዊያን ለመከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ድጋፍ እና የህወሓት የሽብር ድርጊትን የሚያወግዝ ሰልፍ አካሄዱ፡፡

በሰልፉ አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአማራ፣አፋር፣ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በሰላማዊ ዜጎች ላይ የጅምላ ግድያ ማድረሱን የሚያወግዙ መልዕክቶች ተስተጋብተዋል፡፡