Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በደብረ ብርሃን ከ1 ሺህ 500 በላይ ግለሰቦች በሕገ-ወጥ መንገድ ተደራጅተው ተገኙ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በደብረብርሃን ከተማ በተለምዶ 633ቱ የቤት ሕብረት ስራ ማሕበራት በሚል ከተደራጁና ዕውቅና ከተሰጣቸው ማህበራት ውስጥ ከ 1 ሺህ 500 በላይ ግለሰቦች በህገወጥ መንገድ ተደራጅተው መገኘታቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የአስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ደስታ አንዳርጌ ከከተማና ከቀበሌ አመራሮች ጋር በማህበራቱ ጉዳይ መክረዋል።

633ቱ ማህበራት ሲደራጁ 73 የተለያዩ ቦታዎቸ ክፍት የነበሩ ቢሆንም በ65ቱ ክፍት ቦታዎች 1 ሺህ 408 ሰዎች በህገወጥ መንገድ በመደራጀታቸው የከተማው ከንቲባ ኮሚቴ ማህበራቱ ሙሉ በሙሉ እዲሰረዙ መወሰኑ ተገልጿል።

በቀሪ 560 ማህበራት ውስጥም 110 ግለሰቦች በህገወጥ መንገድ ተደራጅተው ተገኝተዋል ያሉት ከንቲባው እነዚህ ግለሰቦች ማሕበራቱ ሳይፈርሱ ግለሰቦችን ብቻ እንዲወጡ መወሰኑን አስረድተዋል።

አሁንም መረጃ የማጣራት ስራው ቀጣይነት እዳለው የገለፁት ከንቲባው በዚህ ህገወጥ ድርጊት ውስጥ የተሳተፉ አካላትን በህግ ለመጠየቅ ይሰራል ብለዋል።

አበበ የሸዋልዑል

 

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version