ስፓርት

የ2020 የቤት ውስጥ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በኮሮና ቨይረስ ምክንያት ተራዘመ

By Tibebu Kebede

January 30, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቻይና አስተናጋጅነት በናንጂንግ ሊካሄድ የነበረውን የ2020 የቤት ውስጥ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሀገሪቱ በተከሰተው በኮሮና ቨይረስ ምክንያት መራዘሙ ተገለፀ።

የ2020 የቤት ውስጥ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በቻይናዋ ናንጂንግ ከተማ አስተናጋጅነት ከፊታችን ከመጋቢት 4 እስከ መጋቢት 6 ድረስ እንደሚካሄድ ነበር የወጣለት መርሃ ግብር የሚያመላክተው።