የሀገር ውስጥ ዜና

የአሸባሪው ቡድን ሀገር የማፍረስ ፍላጎት በኢትዮጵያ ልጆች የተባበረ ክንድ ድባቅ ይመታል-የአፋር ክልል ሴቶች

By Melaku Gedif

July 31, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሸባሪው የህወሓት ቡድን ሀገር የማፍረስ ፍላጎት በኢትዮጵያ ልጆች የተባበረ ክንድ ድባቅ ይመታል ሲሉ የአፋር ክልል ሴቶች ገለጹ።

ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተወጣጡ ሴቶች በሰመራ ከተማ ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ የአሸባሪውን ህወሓት ቡድንን ሀገር የማፍረስ ሴራ ከመከላከያና ልዩ ሀይሎች ጎን በመሰለፍ ለማክሸፍ ቁርጠኛ መሆናቸውን በላቀ የሀገር ፍቅር ስሜት ገልጸዋል።