የሀገር ውስጥ ዜና

በተለያዩ ወንጀሎች ለምርመራና ለክስ የሚፈለጉ 1 ሺህ 600 የሚሆኑ ተጠርጣሪዎችን ለህግ ማቅረብ አልተቻልም- ጠቅላይ አቃቤ ህግ

By Tibebu Kebede

January 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በተለያዩ ወንጀሎች ለምርመራና ለክስ ከሚፈለጉ 3 ሺህ ተጠርጣሪዎች 1 ሺህ 600 ገደማ የሚሆኑትን ለህግ ማቅረብ እንዳልተቻለ የኢፌዴሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ገለፀ።

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው እለት አካሂዷል።