የሀገር ውስጥ ዜና

የወረታ ደረቅ ወደብ በሚቀጥለው ሳምንት ይመረቃል

By Tibebu Kebede

January 25, 2020

አዲስ አበባ ፣ ጥር 16 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የወረታ ደረቅ ወደብ የመጀመሪያ ምዕራፍ በሚቀጥለው ሳምንት ይመረቃል።

የኢትዮጵያ ባህርና ትራንስፖርት ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የወደብና ተርሚናል ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ ስፈጻሚ አቶ እውነቱ ታዬ እንደገለጹት፥ የወደብ ልማቱ ሀገሪቱ ያላትን የደረቅ ወደብ ቁጥር ወደ ስምንት ከፍ ያደርገዋል።