የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር መለስ ዓለም በኬንያ ከኮሎምቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

June 22, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ ዓለም ዛሬ ተቀማጭነታቸውን ኬንያ አድርገው በኢትዮጵያ ከተወከሉት ከኮሎምቢያ አምባሳደር ሞኒካ ግሬፍ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱም በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን መድረኮች የሁለቱን አገሮች ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸውን ኬንያ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!