የሀገር ውስጥ ዜና

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አህመድ መሐመድ ድምጽ ሰጡ

By Tibebu Kebede

June 21, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አህመድ መሐመድ ቡህ በስድስተኛው ሃገራዊ ምርጫ ድምፃቸውን ሰጡ።

በድሬዳዋ አስተዳደር በከዚራ መንደር ሁለት የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፃቸውን የሰጡት አቶ አህመድ በድሬዳዋ ዛሬ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በሠላም እየተካሄደ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ምክትል ከንቲባው ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።

በተሾመ ኃይሉ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!