Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠ/ሚ ዐቢይ የአፍሪካ ቀንን አስመልክተው መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ቀንን አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በመልዕክታቸውም የበለጸገች ሀገር ለመገንባት የሚደረገው ጉዞ በራሱ ፈታኝ ነው፥ ሆኖም በታላቁ አትሌት አበበ ቢቂላ በተግባር እንዳየነው ምቹ የሚባለው መንገድ እንኳ ባዶ እግርን ያቆስላል ብለዋል፡፡

የጉዞውን ስኬታማነት ራዕይን አጥርቶ በማየት እና በ“ባዶ እግርም” ቢሆን ጎዳናውን ሳይለቁ በመገስገስ ይወሰናል ሲሉም በፌስቡክ ገጻቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version