ዓለምአቀፋዊ ዜና

እስራኤል በጋዛ የአልጀዚራና አሶሼትድ ፕሬስ ቢሮዎች የሚገኙበትን ህንፃ አወደመች

By Tibebu Kebede

May 15, 2021

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) እስራኤል በጋዛ የአልጀዚራና አሶሼትድ ፕሬስ ቢሮዎች የሚገኙበትን ህንፃ በአየር ጥቃት አወደመች።

የህንፃው ባለቤት ከእስራኤል የደህንነት መስሪያ ቤት በህንፃው ላይ ጥቃት ሊፈፀም መሆኑን መረጃው ከደረሰው በኋላ ሰዎች ህንፃውን እንዲለቁ አድርጓል።

A tower block that is the base for international media in Gaza has been hit by an Israeli bombardment, causing it to collapse.

People inside were warned about an hour before it was attacked and, at this stage, there are no known casualties.

Read more: https://t.co/aebk62o8nU pic.twitter.com/OZeyD90C0o

— Sky News (@SkyNews) May 15, 2021

ህንፃው በርካታ መኖሪያ ቤቶችን እና ቢሮዎችን የያዘ ነበር።

የእስራኤል ጦር ህንፃው ለፍልስጤሙ ታጣቂ ቡድን ሀማስ ወታደራዊ ድጋፍ የሚያደርጉ ሰዎች ቤት እንደነበር አስታውቋል።

አልጀዚራም ህንፃው ሙሉ በሙሉ ሲወድም በቀጥታ ስርጭት እንዳስተላለፈው ቢቢሲ ዘግቧል።

አሶሼትድ ፕሬስ ባወጣው መግለጫ ፤ የእስራኤል ጦር በህንፃው ላይ የወሰደው እርምጃ አስፈሪ ነው ብሏል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!