Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

1442ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል ከነገ በስቲያ ሐሙስ ይከበራል

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 3 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 1442ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል ከነገ በስቲያ ሐሙስ እንደሚከበር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል።
ምክርቤቱ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬት እንደገለፀው የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ባለመታየቷ 1442ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል ከነገ በስቲያ ሐሙስ ይከበራል ብሏል።
የምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጅ ኡመር ኢድሪስ ምዕመናን በዓሉን ሲያከብሩ የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብ ሊሆን እንደሚገባ ማሳሰባቸው የሚታወስ ነው።
በሀብታሙ ተ/ስላሴ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version