የሀገር ውስጥ ዜና

በሞቀ ቤታቸው ያላቸውን ተቋድሰው ለማክበር ዕድሉን ያላገኙትን ወገኖች በማስታወስ በዓሉን እናክብር – ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ

By Abrham Fekede

May 02, 2021

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ፕሬዚዳንቷ ለመላው የክርስትና እምነቶች ተከታዮች መልካም የብርሃነ ትንስኤ በዓል እመኛለሁ ሲሉ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡

በእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው በሕይወት ሆነው በሞቀ ቤታቸው ያላቸውን ተቋድሰው፤ ለማክበር እንደ እኛ ዕድሉን ያላገኙትን በርካታ ወገኖቻችንን በማስታወስ: በመደገፍና ያለንን በማካፈል እናክብር ሲሉ አሳስበዋ፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!