Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኑሮ ውድነትን ለመቅረፍ መሰረታዊ የምግብ ፍጆታዎች ያለውጭ ምንዛሬ ፈቃድ እንዲገቡ ተወሰነ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኑሮ ውድነት ለመቅረፍ መሰረታዊ የምግብ ፍጆታዎች ያለውጭ ምንዛሬ ፈቃድ እንዲገቡ መፈቀዱን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አስታወቁ፡፡

የንግድና ኢንዱስትሩ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ስኳር፣ምግብ ዘይት፣ስንዴ፣ሩዝ፣የዱቄት ወተት ከውጭ ሀገር እንዲገቡ መወሰኑን በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

በዚህም 250 ሺህ ዶላር (የውጭ ሀገር ገንዘብ) ያላቸው ምንጩን በብሔራዊ ባንክ እያረጋገጡ ማስገባት ይችላሉ ነው ያሉት፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

 

Exit mobile version