የሀገር ውስጥ ዜና

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶውን አስተዋወቀ

By Abrham Fekede

April 01, 2021

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 23፣ 2013 (ኤፍ ቢሲ) ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶውን የማስተዋወቅ መርሀ ግብር አካሂዷል።

ፓርቲው የመጪውን ምርጫ የሚያሸንፍ ከሆነ ማሻሻያ የሚያደርግባቸውን የፖሊሲ አቅጣጫዎች ይፋ አድርጓል።

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ምርጫውን በአብላጫ ድምፅ ካሸነፈ በመጀመሪያ ህገ መንግስቱ እንዲለወጥ ህገ መንግስት አርቃቂ ኮሚሽን እንደሚያቋቁም በማኒፌስቶው መግለጹን ኢቢሲ ዘግቧል።

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፖርቲ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እንደሚሰራም ነው ያስተዋወቀው።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!