የሀገር ውስጥ ዜና

የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አየር ወለድና ኮማንዶ አስመረቀ

By Tibebu Kebede

March 27, 2021

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የ12ኛ ዙር አየር ወለድ ብርጌድና የ34ኛ ዙር ኮማንዶ አስመረቀ፡፡

ተመራቂዎቹ ብላቴ በሚገኘው የልዩ ዘመቻዎች ሃይል ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠናቸውን የተከታተሉ ናቸው፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የሰራዊት ግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ፣ የልዩ ዘመቻዎች ሀይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሹማ አብደታ እና የሪፐብሊካን ጋርድ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ብርሀኑ በቀለ ተገኝተዋል፡፡

ተመራቂዎቹ በስልጠና ቆይታቸው ያገኙትን ትምህርት በተግባር የተደገፈ ትርኢት ማሳየታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!