Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፋኦ በምስራቅ አፍሪካ የበረሃ አንበጣ መንጋ መቀነሱን አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 17 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ምግብ እና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) በምስራቅ አፍሪካ የበረሃ አንበጣ መንጋ መቀነሱን አስታወቀ፡፡

ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያና ኬንያን ጨምሮ በቀጠናው የዝናብ አለመኖር ለበረሃ አንበጣው መቀነስ ምክንያት መሆኑን ገልጿል፡፡

በአካባቢው ያለው ዝቅተኛ የዝናብ መጠን ከሚደረገው ቁጥጥር ጋር ተያይዞ የአንበጣ መንጋው እንዳይፈለፈል አድርጎታልም ነው ያለው፡፡

ዝናብ አምጭ ሁኔታዎች ካለመስተዋላቸው ጋር ተያይዞ ሁኔታዎች በዚሁ ሊቀጥሉ እንደሚችሉም ነው የገለጸው፡፡

ከዚህ ባለፈ ግን የአንበጣ መንጋውን ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለውን ቁጥጥር ማጠናከር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

አሁን ላይ በኬንያ አንዳንድ አካባቢዎች እና በታንዛኒያ ድንበር አካባቢ ኩብኩባ መታየቱንም ጠቅሷል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version