Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሞዛምቢክ አየር መንገድ ወደ ኬንያ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 10 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሞዛምቢክ አየር መንገድ ወደ ኬንያ የሚያደርገውን በረራ ለጊዜው ማቋረጡን አስታወቀ፡፡
አየር መንገዱ ከኬንያ ወደ ሞዛምቢክ እንዲሁም ከሞዛምቢክ ወደ ኬንያ የሚደረገውን በረራ ማቋረጡን ነው ያስታወቀው፡፡
ይህ ውሳኔም በአሰራር ምክንያት የተላለፈ መሆኑም ተነግሯል ፡፡
አየር መንገዱ ዝርዝር መግለጫ ባይሰጥም ውሳኔው በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ከአየር ትራንስፖርት መቀዛቀዝ ጋር የተቆራኘ ነው ተብሎ ይታሰባል ፡፡
ከዚህ ቀደም አየር መንገዱ በወረርሽኙ ምክንያት የተወሰነ የሃገር ውስጥ በረራዎችን መቋረጡ የሚታወስ ነው፡፡
ምንጭ፡-ቢቢሲ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version