የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ከዩ ኤን ኤድስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጋር ተወያዩ

By Abrham Fekede

March 18, 2021

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2013(ኤፍቢሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ከዩኤንኤድስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጋር ተወያዩ፡፡

ፕሬዚዳንቷ በበኤች አይቪ ኤድስ ላይ ከሚሰራው የተመድ አካል /ዩኤንኤድስ/ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን ጋር ነው የተወያዩት፡፡

በውይይታቸው ድርጅቱ እየሰራቸው በሚገኙ ስራዎች ዙሪያ መክረዋል፡፡

በሂደትም በኢትዮጵያ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በተያዙ ዕቅዶች ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ከፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!