Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በጂቡቲ የተገነባው የኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች ማቆሚያ ተመረቀ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጂቡቲ የተገነባው የኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች ማቆሚያ ተመረቀ፡፡

የትራንስፖርት ሚኒስትር ዲኤታው አቶ አወል ወግሪስ የተሽከርካሪ ማቆሚያው ግንባታ እያደገ ከመጣው የወጪ ገቢ እቃዎች አንጻር እየጨመረ የመጣውን የአገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት መንግስት ያለውን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለውታል፡፡

ከዚህ ባለፈም የሁለቱ እህትማማች ሃገራት ግንኙነት በኢኮኖሚያዊ ትስስር እየተጠናከረ መሄዱን ያሳያልም ነው ያሉት፡፡

የጁቡቲ መንግስት ለማቆሚያው እና ለማስፋፊያው ግንታ ላደረገው ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

የትራንስፖርት ሚኒስቴር ያስገነባው የተሽከርካሪ ማቆሚያ ግንባታ መጠናቀቅ፥ የተሽከርካሪዎችን መጨናነቅን በማስቀረት የተሳለጠና ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡

በምርቃት መርሃ ግብሩ ላይ የትራንስፖረት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ አወል ወግሪስ፣ በጂቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ፣ የጂቡቲ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ሚኒስትር ሙሳ ሞሃመድና የሃገራቱ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version