የሀገር ውስጥ ዜና

የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ ገቡ

By Tibebu Kebede

February 06, 2021

አዲስ አበባ ፣ ጥር 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሌክስ ሺሴኬዲ አዲስ አበባ ገቡ፡፡

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው ለፕሬዚዳንቱ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ፕሬዚዳንቱ ከደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነትን ሃላፊነት እንደሚቀበሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!