የሀገር ውስጥ ዜና

አየር መንገዱ ኮቪድ-19 ያስከተለውን ተፅእኖ ተቋቁሞ በማለፍ ከኤርባስ ሽልማት ተበረከተለት

By Tibebu Kebede

December 16, 2020

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኮቪድ-19 ያስከተለውን ተፅእኖ ተቋቁሞ በማለፍ ከኤርባስ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ሽልማት ተበከተለት።

አየር መንገዱ በአቪዬሽኑ መስክ ላስመዘገበው ስኬት እና ሙያዊ ብቃት እውቅና እና ሽልማቱ እንደተሰጠው ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማሪያም ሽልማቱን የኤርባስ የአፍሪካ የሽያጭ ምክትል ፕሬዚዳንት ሃዲ አኮም በዛሬው እለት በአየር መንገዱ ቅጥር ግቢ በመገኘት አበርክተዋል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!