Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ በተጠረጠረበት ወንጀል ፍርድ ቤት ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ በተጠረጠረበት ወንጀል ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡

ተጠርጣሪው ጋዜጠኛ የተዛባ መረጃ በማውጣትና ግጭት በመቀስቀስ ህገ መንግስትና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ለመናድ ሲንቀሳቀስ ነበር በማለት መርማሪ ፖሊስ ለችሎቱ አስረድቷል፡፡

ፖሊስ በተጠርጣሪው ላይ የጀመርኩትን ምርመራ ለማከናወን ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል ብሏል፡፡

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ አንደኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ዳኛ ለፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ ያስፈልገዋል በሚል የ13 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በታሪክ አዱኛ

Exit mobile version