የሀገር ውስጥ ዜና

ለፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የአየር ሰዓት ድልድል ለማውጣት ዝግጅት ተደርጓል

By Tibebu Kebede

December 30, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውን እና ዓላማቸውን በመገናኛ ብዙሃን ለህዝቡ እንዲያስተዋውቁ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአየር ሰዓት ድልድል ለማውጣት መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ገለፀ።

በኢትዮጵያ በጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ ወቅት የመገናኛ ብዙሃን የአየር ሰዓት ስርጭታቸውና ከህትመት ገፃቸው ለፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ ያውላሉ።