የሀገር ውስጥ ዜና

የመምህራን ቀን ዓመታዊ በዓል አውደ ጥናት ተካሄደ

By Abrham Fekede

October 30, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 20፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የመምህራን ቀንን “መምህራን ቀውስ ለመቀልበስም ሆነ ለመጭው ጊዜ ብሩህነት ግንባር ቀደም ሚና አላቸው” በሚል መሪ ቃል ትምህርት ሚኒስቴር ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ያዘጋጁት አውደ ጥናት በባህር ዳር ተካሄደ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ በአውደ ጥናቱ ላይ አሁን እየታዩ ያሉ ሀገራዊ ችግሮችን ለመቅረፍ ግብረገብነት ያለው፣ ብዝሃነትንና አንድነትን የሚያስተናግድ ትውልድ ለማፍራት እንደሚሰራ አንስተዋል።