አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የእንቦጭ አረምን ከጣና ሐይቅ ለማስወገድ ለአንድ ወር የተላለፈውን ሀገራዊ ዘመቻን ተከትሎ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጣና ተገኝተዋል።
በዘመቻው ከሚኒስትሯ በተጨማሪ ከህዝብ ተወካዮች የከተማ ልማት፣ ኮንስትራክሽንና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራርና አባላት፣ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር፣ የትራንስፖርት ዘርፍ ተጠሪ ተቋማት ዳይሬክተሮች እና የሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች በዘመቻ እየተሳተፉ ይገኛሉ።