የሀገር ውስጥ ዜና

በቀላል ባቡር መንገድ መሸጋገሪያዎች ላይ የሚታየውን የትራፊክ ፍሰትና የደህንነት ችግር ለመቅረፍ ያለመ ውይይት ተካሄደ

By Tibebu Kebede

October 22, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ የቀላል ባቡር መንገድ መሸጋገሪያዎች ላይ የሚታየውን የትራፊክ ፍሰትና የደህንነት ችግር መቅረፍ ላይ ያተኮረ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተካሂዷል።

ውይይቱን የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የከተማዋን የትራፊክ እንቅስቃሴ ሰላማዊና ተቀባይነት ያለው እንዲሆን እንዲሁም በቀላል ባቡር መንገድ ላይ ማሻሻያዎችን ለማካሄድ በማለም ነው ያካሄደው።