የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ በግለሰብ ቤት የተከማቸ ከ2 ሚሊየን በላይ አዲሱ የብር ኖት ተያዘ

By Meseret Demissu

October 22, 2020

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በግለሰብ ቤት ውስጥ የተከማቸ ከ2 ሚሊየን በላይ አዲሱ የብር ኖት መያዙን ፖሊስ አስታወቀ።

ጥቅምት 7 ቀን 2013 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ዶምቦስኮ ትምህርት ቤት አካባቢ በግለሰብ ቤት ውስጥ የተከማቸ ገንዘብ ስለመኖሩ ህብረተሰቡ ለፖሊስ ባደረሰው መረጃ መሠረት መያዙ ተገልጿል።