የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ በስፖንጅ ፋብሪካ ውስጥ የተነሳ እሣት ንብረት አወደመ

By Meseret Demissu

October 22, 2020

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 12 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ በስፖንጅ ፋብሪካ ውስጥ የተነሳ እሣት ከ500 ሺህ ብር በላይ ግምት ያለው ንብረት ማውደሙን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለፀ።

በክፍለ ከተማው ወረዳ 3 ራስ ደስታ አካባቢ በአንድ ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ባረፈ ስፖንጅ ፋብሪካ ላይ የተነሳው የእሣት አደጋ መንስኤው አልታወቀም።