Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ታጣቂዎች 900 እስረኞችን አስለቀቁ

GOMA, CONGO - APRIL 26: Congolese soldiers (FARDC) stand guard April 26, 2010 on the outskirts of Goma, Democratic Republic of Congo. Government soldiers, who usually get paid around $35-40 per month, are struggling to survive and support their family. Some of them are accused of extortion, rape, and other crimes. (Photo by Kuni Takahashi/Getty Images)

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ቤኒ ከተማ ታጣቂዎች 900 እስረኞችን ማስለቀቃቸው ተገለፀ።

ከካንግባዩ እስር ቤት ካመለጡት 900 እስረኞች መካከል የታጣቂ ቡድን አባላት እንደሚገኙበት ቢቢሲ የከተማዋን ከንቲባ ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

አሁን ላይ 110 የሚሆኑ ወንጀለኞች በእስር ቤቱ እንደሚገኙ የተነገረ ሲሆን ታጣቂዎቹ እስረኞችን ማስለቀቅ የሚያስችሉ ቁሳቁሶችን ይዘው ነበር ተብሏል።

የቤኒ ከተማ ከንቲባ ሞዴስቴ ባክዋናምሃ ለተፈጸመው ድርጊት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎችን ተጠያቂ አድርገዋል።

ከእስር ቤቱ ካመለጡት በከተማዋ የተደበቁ ሊኖሩ እንደሚችሉ የተገመተ ሲሆን የከተማ ነዋሪም ድርጊቱን እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።

Exit mobile version